የበሽታዎች ስርጭት በምንዱባን መንደር
ማክሰኞ፣ መጋቢት 16 2000
በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ በምትገኘዉ ጎስቋላ መንደር በመታሬ ተፋፍጎ የሚኖረዉ ህዝብ ለሳንባ ነቀርሳና መሰል ተላላፊ በሽታዎች የተጋለጠ ነዉ። በስፍራዉ ለህዝቡ የጤና አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘዉ የፈረንሳዩ ድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን ባንደረባ የአኗኗር ሁኔታዉ እሷ ከምታዉቀዉ የተለየ በመሆኑ ቢያስገርማትም፤፡ በሙያዋ የምትችለዉን ሁሉ እያደረገች ትገኛለች።