1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የበዓል ገበያ በአሶሳ

ነጋሣ ደሳለኝ
ረቡዕ፣ ጳጉሜን 5 2017

በመሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ዋጋ ላይ የጎላ ጭማሪ ባይኖርም አሁን ያለው ወቅታዊ ዋጋ ከፍተኛ መሆኑ በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ላይ እንደሚያሳድር ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

የአሶሳ ከተማ የዓመት በዓል ገበያ በከፊል።አሶሳ ከተማ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ገበያ  ከዚህ ቀደም ከነበረው ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ የቁም እንስሳ ለሽያጭ ቀርቧል
የአሶሳ ከተማ የዓመት በዓል ገበያ በከፊል።አሶሳ ከተማ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ገበያ ከዚህ ቀደም ከነበረው ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ የቁም እንስሳ ለሽያጭ ቀርቧልምስል፦ Negassa Desalegn/DW

የበዓል ገበያ በአሶሳ

This browser does not support the audio element.


በበኒ ሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማየአዲስ ዓመት ዋዜማ ገበያ  ከዚህ ቀደም ከነበረው ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ የቁም እንስሳ ለሽያጭ ቀርቧል። ነዋሪዎች እንዳመለከቱት የበግ ዋጋ ከለፈው ዓመት ጋር ሲናጻጸር ዋጋ ጨምሯል፡፡ በሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ላይ ደግሞ መጠነኛ ጭማሪዎች ቢኖሩም የጎላ የዋጋ ለውጥ አለመታየቱን አመልክተዋል፡፡ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በበኩሉ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ እየተቆጣጠረ መሆኑን አስታውቋል፡፡
 

‹‹በቁም እንስሳት ላይ ዋጋ ጭማሪ ተስተውሏል››   

በመሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ዋጋ ላይ የጎላ ጭማሪ ባይኖርም  አሁን ያለው ወቅታዊ ዋጋ ከፍተኛ መሆኑ በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ እንደሚያሳድር ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡  ለበዓል ውሎ የሚረዱ ከዶሮ ጀምሮ ያሉ ግብአቶችን በመጥቀስ ወቅታዊ የገበያውን ሁኔታ ያነጋገርናቸው ሁለት ነዋሪዎች እንደሚከተው አብራርተዋል፡፡
 

ከኦሳሳ ከተማ ሸማቾች አንዱ።ነዋሪዎች እንዳመለከቱት የበግ ዋጋ ከለፈው ዓመት ጋር ሲናጻጸር ዋጋ ጨምሯል፡፡ በሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ላይ ደግሞ መጠነኛ ጭማሪዎች ቢኖሩም የጎላ የዋጋ ለውጥ አልመታየቱን አመልክተዋልምስል፦ Negassa Desalegn/DW

‹‹ምክንያታዊ ያልሆነ ዋጋ የጨመሩ ግለሰቦቸ ተቀጥተዋል››

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ አሶሳ ከተማን ጨምሮ በሁሉም የክልሉ ከተሞች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አካላትን ቁጥጥር እያደረገ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡ የቢሮ ኃላፊ አቶ አሲር ኢብራሂም ህግ ወጥ ንገድና ምክንያታዊ ያልሆነ ዋጋ ጭማሪ የሚቆጣጠሩ ግብር ሀይል በስራ ላይ እንደሚገኝ የተናገሩ ሲሆን እስካሁን የታየ የጎላ የዋጋ ጭማሪ አለመኖሩን ገልጸዋል፡፡

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ 200 የሚደርሱ ያለአግባብ ዋጋ ጨምረዋል የተባሉ ግለሰቦችን መቅጣቱንም አመልክተዋል፡፡ በዛሬው የአሶሳ ገበያው ውሎም ከአጎራባች ክልሎችም በርካታ የቁም እንስሳት ለገበያ መቅረቡም ተገልጸዋል፡፡

ነጋሳ ደሳለኝ

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ሥለሺ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ
ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW