የበጀት ቀመር ድልድል አዋጅ
ረቡዕ፣ የካቲት 27 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የፌደሬሽን ምክር ቤት እስካሁን የበጀት ክፍፍል የሚያደርግ ቀመር ለ 7 ጊዜ ያዘጋጀና እያሻሻለ ጥቅም ላይ ያዋለ ቢሆንም ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ እንዳልነበረው ነው የሚነገረው ፡፡ ይህም በመሆኑ ከተለያዩ አካላት የበጀት ፍትሃዊነት ጥያቄዎች እንዲነሱና ክልሎች ተደጋጋሚ የበጀት ድጎማ እና የገንዘብ ጥያቄዎችን እንዲያነሱ ሲያደርጋቸው ቆይቷል ። ላለፉት 3 አመታት ሲያገለግል የነበረው የበጀት ቀመር ድልድል እስከ 2012 ብቻ የሚያገለግል ሲሆን የፌዴራል እና የክልል መንግስታት የሃብት ክፍፍልን የተመለከተው ጉዳይ ፍተሻ እየረደረገበት በመሆኑ አሰራሩን የሚመለከት በአዋጅ ደረጃ የሚወጣ ህግ ለማዘጋጀት ምክክር እየተደረገ ነው ።ሕጉ ውይይት ከተደረገበት በሁዋላ በአሰራሩ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በሚያስወግድ መንገድ ተዘጋጅቶ ይቀርባል ተብሏል፡፡ የአዲስ አበባው ወኪላችን ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝር ዘገባ አለው።
ሰሎሞም ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ተስፋለም ወልደየስ