የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮች አቤቱታ
ማክሰኞ፣ ግንቦት 24 2013![Äthiopien Vertreibung und Massaker in der Region West-Benishangul Gumuz](https://static.dw.com/image/56453683_800.webp)
ማስታወቂያ
ከቤኒሻንል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ሰዳል ወረዳ የተከሰተዉን የፀጥታ መታወክ ሸሽተዉ ምዕራብ ወለጋ መንዲ እና አካባቢዉ የሠፈሩ ተፈናቃዮች የአስቸኳይ ጊዜ ርዳታ ባለማግኘታቸዉ ለችግር መጋለጣቸዉን አስታወቁ።በሰዳል ወረዳ የተፈጠረዉን ግጭት ሸሽተዉ ምዕራብ ወለጋ የገቡት ተፈናቃዮች ወደ ሶስት ሺሕ ይጠጋሉ። የአሶሳዉ ወኪላችን ነጋሳ ደሳለኝ በስልክ ያነጋገራቸዉ ተፈናቃዮች እንደሚሉት ባለፈዉ ሚያዚያ መጀመሪያ ከየቀያቸዉ ከተፈናቃሉ ወዲሕ ምግብ፣መድሐኒትም ሆነ መጠለያ አግኝተዉ አያዉቁም።የቤኒሻንል ጉሙዝ ክልል የአደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ባለስልጣናት እንዳሉት መስሪያ ቤታቸዉ በክልላቸዉ ለሰፈሩ ተፈናቃዮች እንጂ ከክልሉ ዉጪ ኦሮሚያ ክልል ለሠፈሩ ተፈናቃዮች ርዳታ የማቅረብ ኃላፊነትም ሕጋዊ መብትም የለዉም።
ነጋሳ ደሳለኝ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ