የብሪታንያ ጥያቄ በአውሮጳ ኅብረት25 ጥር 2008ረቡዕ፣ ጥር 25 2008የአዉሮጳ ሕብረት፤ ብሪታንያ ከሕብረቱ አባልነት እንዳትወጣ ለማሳመን ይረዳል ያለዉን የመደራደሪያ ረቂቅ ይፋ አደረገ። የሕብረቱ ኮሚሽን ፕሬዝደንት ዶናልድ ቱስክ ለአባል ሐገራት ያሠራጩት ረቂቅ ብሪታንያ በአባልነት እንድትቆይ የሐገሪቱ መንግሥት ላቀረበዉ ጥያቄ አወንታዊ መልስ የሚሰጥ ነዉ።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግምስል picture-alliance/dpaማስታወቂያ[No title]This browser does not support the audio element. ረቂቁን የብሪታንያዉ ጠቅላይ ሚንስትር ዴቪድ ካሜሩን «አርኪ» ቢሉትም ከብሪታንያም፤ ከሌሎች የሕብረቱ አባል ሐገራት ፖለቲከኞም ተቃዉሞ ገጥሞታል።ብሪታንያ የአዉሮጳ ሕብረት አባል እንደሆነች እንድትቀጥል ወይም እድትወጣ የሐገሪቱ ሕዝብ በመጪዉ ሰኔ በሚሰጠዉ ድምፅ ይወስናል። ገበያዉ ንጉሴ ማንተጋፍቶት ስለሺ ነጋሽ መሐመድ