1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተመድ የኤርትራ ማዕቀብ መነሳት

ቅዳሜ፣ ኅዳር 8 2011

ይህ አሁን የተነሳው ማዕቀብ እና የተነሳበት ምክንያት እንዲሁም በኤርትራ እና የአፍሪቃ ቀንድ ሀገሮች ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነቶች ላይ የሚኖረው አንደምታ ምን ይሆን?

UN-Sicherheitsrat in New York | Debatte Sanktionen gegen Eritrea
ምስል picture-alliance/Xinhua News Agency/L. Muzi

This browser does not support the audio element.

የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ላለፉት ዘጠኝ አመታት በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ያነሳ መሆኑን ባለፈው ዕሮብ አስታውቋል። ምክር ቤቱ ኤርትራ አሸባብ የተባለውን ቡድን ትረዳለች በሚል እና ከጅቡቲ ጋርም ባላት የድንበር ውዝግብ ምክንያት እኢአ በ 2009 ዓ ም በተለይ በጦር መሣሪያ ግዥ ማዕቀብ እና በተወሰኑ ባለስልጧኖቿ ላይም የጉዞ እገዳ እንዲደረግ እና የባንክ ሒሳባቸውም እንዳይንቀሳቀስ ውሳኔ ማሳለፉ የሚታወስ ነው። ይህ አሁን የተነሳው ማዕቀብ እና የተነሳበት ምክንያት እንዲሁም በኤርትራ እና የአፍሪቃ ቀንድ ሀገሮች ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነቶች ላይ የሚኖረው አንደምታ የዛሬው የትኩረት በአፍሪቃ ዝግጅት የሚዳስሰው ነው።

ገበያው ንጉሴ

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW