1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የተመ ድርጅት ስለ ዩክሬን ጦርነት ማን ማድረግ ይቻለዋል?

ሰኞ፣ የካቲት 21 2014

ከ40 አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠራው የተ.መ.ድ ጠቅላላ ጉባኤ የሩሲያን የዩክሬን ወረራ ለማውገዝ የተዘጋጀ የውሳኔ-ሐሳብ ይቀርብለታል። የውሳኔ ሐሳቡ ወደ ጠቅላላ ጉባኤው የተመራው ጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ ቀርቦ በሩሲያ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ውድቅ ከሆነ በኋላ ነው። የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ስለ ዩክሬን ጦርነት ማን ማድረግ ይቻለዋል?

USA I United Nations General Assembly
ምስል፦ Seth Wenig/dpa/picture alliance

ከገበያው ንጉሴ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

This browser does not support the audio element.

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በሩሲያ የዩክሬን ወረራ ላይ ለመወያየት ዛሬ ይሰበሰባል። ጉዳዩ ወደ ጠቅላላ ጉባኤው የተመራው በጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ ሲሆን የሩሲያን ወረራ ለማውገዝ የተዘጋጀ የውሳኔ ሐሳብ ይቀርብለታል። ጠቅላላ ጉባኤው አስቸኳይ ስብሰባ ሲያደርግ በ40 አመታት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የድርጅቱ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤትም በዩክሬን ጥያቄ በጉዳዩ ሊወያይ ዝግጅት ላይ ነው።

ዩክሬን የአውሮፓ ኅብረትም ሆነ የኔቶ አባል ባትሆንም ከኅብረቱ አባል አገራት በተናጠል እና በጋራ ድጋፍ እያገኘች ትገኛለች። የሩሲያ ወረራ ከዚህ ቀደም ገለልተኛ የሚባሉ እንደ ስዊትዘርላድ ያሉ አገሮችን ጭምር ለዩክሬን እንዲያግዙ አስገድዷል። የአውሮፓ አገራት በርከት ያሉ ማዕቀቦች በሩሲያ፣ በባለሥልጣኖቿ እና በተቋማቷ ላይ እየጣሉ ነው። 

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለዩክሬን ምን ማድረግ ይቻለዋል? የአውሮፓ አገራት ለሩሲያ ወረራ በተናጠል እና በኅብረት የሰጧቸው ምላሾች ምን ፈየዱ? የብረስልሱ ወኪላችንን አነጋግረነዋል።  

ገበያው ንጉሴ

እሸቴ በቀለ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW