1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የኢድ አል አደሃ በዓል መልዕክት

ቅዳሜ፣ ሐምሌ 10 2013

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በመጪው ሳምንት የሚከበረውን የኢድ አል አደሃ በዓል መልዕክት በማስመልከት ዛሬ ቅዳሜ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Äthiopien | Mufti Haji Umer Idris
ምስል፦ Solomon Muchie/DW

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የኢድ አል አደሃ በዓል መልዕክት

This browser does not support the audio element.

የመስዋዕትነት በዓል በሚል የሚጠራው የ ኢድ አል አደሃ ዓረፋ በዓል በእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ዘንድ በመጪው ማክሰኛ በልዩ ልዩ ሥነ ሥርዓቶች ይከበራል።

በዓሉን አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ የሰጡት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ኢትዮጵያውያን ወደ አንድነት እንዲመጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዓሉ በሰላምና በመረዳዳት እንዲከበር የጠየቁት ተቀዳሚ ሙፍቱ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በብሔረሰብ መለያየት መወገዝ አለበት ብለዋል።
ጦርነት፣ አመፅ አይጠቅምም ያሉት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ወደ ሰላምና አንድነት እንመለስ አገራችንንም ከማጥፋት እንቆጠብ በማለት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥሪ አቅርበዋል። 

ሰለሞን ሙጬ

እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW