ትናንት ብራሰልስ ቤልጂግ በሚገኘው የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፊት ለፊት ሰልፍ የወጡት ኢትዮጵያውያን በቅርቡ የተካሄደውንና የአንድ ፓርቲ የበላይነት የተረጋገጠበትን የኢትዮጵያ ምርጫ የአውሮፓ ህብረት እንዲያወግዝ ጠይቀዋል ። ሰልፈኞቹ ይህንኑ ጥያቄአቸውን ለህብረቱ ባለሥልጣናት በፅሁፍ አቅርበዋል ። የብራሰልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴ በስፍራው ተገኝቶ ነበር ። ገበያው ንጉሴ --
ሂሩት መለሰ
ተክሌ የኋላ