የተቃውሞ ሰልፍ በአፋር ክልል
ሰኞ፣ ጥር 14 2004ማስታወቂያ
በአፋር ክልል የኩንባ ወረዳ ነዋሪዎች በአርትአሌ ታግተው የተወሰዱ ሁለት ኢትዮጵያውያን እና ሁለት ጀርመናውያን በአስቸኳይ እንዲፈቱ በሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ጠይቀዋል። ሰልፈኞቹ በንጹሃን ሀገር ጎብኚዎች ላይ የተፈፀመውን የጥቃት ርምጃ በመኮነን አስፈላጊው ርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። ተመሳሳይ ሰልፎች በመጋሌ፣ አርፒቲ እና በሌሎች የአፋር ክልል ወረዳዎች ተካሂደዋል።
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሄር
አርያም ተከሌ
ሸዋዬ ለገሰ