የተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ
ሰኞ፣ ነሐሴ 8 2015![የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት](https://static.dw.com/image/66529667_800.webp)
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሳምንት በፊት የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአብላጫ ድምጽ ዛሬ አጸደቀ። አዋጁን 16 የፓርላማ አባላት ሲቃወሙት፤12 አባላት ደግሞ ድምጽ ከመስጠት ታቅበዋል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሐምሌ 28፤ 2015 ዓ.ም በሙሉ ድምጽ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፤ በአማራ ክልል እና “እንዳስፈላጊነቱ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች” ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማጽደቅ ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት የተገኙት አባላት ከፍተኛ ክርክር እና በርካታ ነጥቦችን ማንሳታቸዉ ተመልክቷል
ኢሰመኮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በአማራ ክልል ብቻ እንዲወሰን ለመንግስት ጥሪ አቀረበ
አዋጁ የተደነገገው "በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሚታየውን በትጥቅ የተደገፈ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ በመደበኛ የሕግ ማስክበር ሥርዓት ለመቆጣጠር ወደ ማይቻልበት ደረጃ የተሸጋገረ በመሆኑ" እንደሆነ መንግሥት ማስታወቁ ይታወቃል
እስራኤል ከ200 በላይ የሚሆኑ ዜጎቿን ከአማራ ክልል አወጣች
ምክር ቤቱ በዛሬው ስብሰባው ሰባት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ አባላትን በመሰየም አፅድቋል።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ አባላቱ፤አቶ አዝመራው አንዴሞ ሰብሳቢ፤ ወ/ሮ ነጃት ግርማ ዶ/ር ምክትል ሰብሳቢ፤ አቶ ሣዲቅ አደም አባል፤ አቶ መስፍን እርካቤ አባል፤ ዶ/ር አብርሃም በርታ አባል
ወ/ሮ ፍሬህይወት ተሾመ አባል፤ አቶ ወንድሙ ግዛው ናቸዉ። ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተሰየሙት የመርማሪ ቦርድ አባላት በጉባዔው ፊት ቃለ ማህላ መፈጸማቸውም ታዉቋል።
ሰለሞን ሙጬ
አዜብ ታደሰ