የኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ቡድን የቱሪዝም መድረክ በፓሪስ
ዓርብ፣ ሐምሌ 26 2016![ፓሪስን ያደመቀው የኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ቡድን የቱሪዝም መድረክ](https://static.dw.com/image/69841106_800.webp)
ማስታወቂያ
ሰሞኑን ፓሪስ እየደመቀች የምትገኘው በማስተናገድ ላይ ባለችው የፓሪስ 2024 የኦሎምፒክ ብቻ አይደለም። በፓሪስ ኦሎምፒክ የምትሳተፈው ኢትዮጵያ ከአትሌቶቿ ባሻገር በጎዳና ባህላዊ የቡና ማፍላት ሥርዓት የታጀበ የኢትዮጵያን ባህልና ታሪካዊ የቱሪስት መስህቦችን በሚያስተዋውቅ፤ ለዚህም ሌላ የኢትዮጵያን የኦሎምፒክ ጀግኖች ፎቶዎች ባካተተው ልዩ ዝግጅትም ነው። ይህ ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ በሚል ስያሜ በፓሪስ ፈረንሳይ እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያን ገጽታ የማስተዋወቅ ልዩ ዝግጅት በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ፣ በኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር እና ፓሪስ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስተባባሪነት የዘጋጀ መሆኑን ከፓሪስ ዘጋቢያችን ሃይማኖት ጥሩነህ የላከችው ዜና ያስረዳል።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ