የቱርክ ፕሬዝዳንት ጉብኝት በኢትዮጵያ
ሐሙስ፣ ጥር 14 2007ማስታወቂያ
የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሴፕ ጠይብ ኤርዶኻን በሠወስት የአፍሪቃ ቀንድ ሐገራት የሚያደረጉትን ጉብኝት ትናንት ከኢትዮጵያ ጀምረዋል።በርካታ የቱርክ የኩባንያ ባለቤቶችን፤ የድርጅት ተጠሪዎችንና ነጋዴዎችን ያስከተሉት ኤርዶኻን ዛሬ ከኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚንስትር ከአቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ ጋር ተነጋግረዋል።ሁለቱ መሪዎች በጋራ ለሁለቱ ሐገራት የኩባንያ ባለቤቶች፤ የድርጅት ተጠሪዎችና ነጋዴዎች ገለፃና ማብራሪያ ሰጥተዋልም።ኤርዶኻን ከኢትዮጵያ ሌላ ሶማሊያና ጀቡቲን ይጎበኛሉ።ሥለ አዲስ አበባ ጉብኝታቸዉ ወኪላችንን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስን በሥልክ አስርድቶናል።
ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ