« መፍትሔዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ነዉ» ኦፌኮ
ዓርብ፣ የካቲት 30 2010ማስታወቂያ
የዩናይትድ ስቴትሱ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ሬክስ ቲለርሰን አዲስ አበባን በጎበኙበት ወቅት የተቃዋሚዉን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ባለሥልጣናትን እንዳላነጋገሩ የፓርቲዉ መሪዎች አስታወቁ።የኦፌኮ ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ሙላቱ ገመቹ እንዳሉት የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ቀዉስ የሚወገደዉ በኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ በዉጪ ኃይል አይደለም።ካለፈዉ አርብ ጀምሮ በተደረገዉ አድማ እና ተቃዉሞ ሰበብ በሰዉ ሕይወት አካል እና ሐብት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንም አቶ ሙላቱ አስታዉቀዋል።አቶ ሙላቱን በስልክ አነጋግሬያቸዋለሁ።
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ