1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የ«ታላቊ የሕዳሴ ግድብ» የሦስትዮሽ ድርድር

ቅዳሜ፣ ሰኔ 6 2012

ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ በምታስገነባዉ ግዙፍ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመጫ «የታላቊ ሕዳሴ» ግድብ ያወዛገባቸው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ ባለስልጣናት ስለ ግድቡ የዉኃ አሞላል በዚህ ሳምንት በተከታታይ ቀናት በቪዲዮ ጉባኤ ተወያይተዋል።

Äthiopien Addis Abeba | Report | Grand Ethiopian Renaissance Dam
ምስል፦ DW/N. Desalegen

ኢትዮጵያ የውጭ አካላት ሚና የተገደበ እንዲኾን ትፈልጋለች

This browser does not support the audio element.

የ«ታላቊ የሕዳሴ ግድብ» የሦስትዮሽ ንግግር በኢትዮጵያ፤ ግብፅ እና ሱዳን መካከል ዳግም መከናወን ጀምሯል። ውይይቱን በተመለከተ የኢትዮጵያ የውኃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚንሥትር ሐሙስ ዕለት ባወጣው መግለጫ፦ድርድሩ ከኹለት ቀናት በኋላ ቅዳሜ ዳግም እንደሚጀምር ገልጦ ነበር። በመግለጫውም ኢትዮጵያ የታችኛው ተፋሰስ ኹለቱ ሃገራትን ማለትም ሱዳን እና ግብፅን የመጎዳት ዓላማ እንደሌላት ጠቅሷል።

ይልቊንም ኢትዮጵያ የሦስቱንም ሃገራት ሕዝቦች የጋራ ጥቅም የሚያስጠብቅ ብቸኛው መንገድ የቴክኒካል ድርድሩ ላይ ነው ያለው ብላለች። ሦስቱም ሃገራት በጥሩ መተማመን እና ቊርጠኝነት የጋር ጥቅም የሚያስገኝ ውጤት ላይ ለመድረስ የመሥራቱን አስፈላጊነት ኢትዮጵያ ያሰመረችበት መኾኑንም ጠቅሷል። ግድቡ ውኃ መሞላት የሚጀምርበትን የመጀመሪያ ጊዜ እና ዓመታዊ አለቃቅን በተመለከተ ታዛቢዎች በተገኙበት የተከናወነውን የቪዲዮ ጉባኤ ድርድር ሐሙስ ዕለት የመራችው ኢትዮጵያ ናት። የቅዳሜውን የቪዲዮ ጉባኤ ሱዳን እንደምትመራው ተገልጧል።  

ምስል፦ DW/Negassa Desalegen

በድርድሩ ከሦስቱ ሃገራት የውኃ የመስኖ እና ኢነርጂ ሚንስትሮች በተጨማሪ ቀደም ሲል ታዛቢ ተብለው ወደ አደራዳሪነት ሚናቸውን ከቀየሩት ዩናይትድ ስቴትስ እና የዓለም ባንክ መካከል ዩናይትድ ስቴትስ ዳግም ተገኝታለች። በተጨማሪም ደቡብ አፍሪቃ እና የአውሮጳ ኅብረት ታዛቢዎች ነበሩ። ኢትዮጵያ ሐሙስ ዕለት ዳግም  የጀመረው ንግግር ላይ የውጭ አካላት ሚና የተገደበ እንዲኾን ትፈልጋለች ሲል የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። በባለፈው የዋሽንግተን ንግግር የዩናይትድ ስቴትስ ጣልቃ ገብነት እና ጫና ኢትዮጵያ በመጨረሻው ሰዓት ከድርድሩ እንድትቀር ማድረጉም ይታወሳል።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW