1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የታዳሽ ኃይል ፍላጎት ሊጨምር መቻሉ

ረቡዕ፣ ኅዳር 15 2008

የዓለም ቀፍ የታዳሽ ኃይል ተቋም « IRENA » የዓለም የታዳሽ ኃይል ፍላጎት በ2030 በሁለት እጥፍ እንደሚጨምር በቅርቡ ይፋ ባደረገዉ ጥናት አሳይቷል። በዚህም የተነሳ፣ በአካባቢዉ ያሉ ባለሙያዎች አፋጣኝ የኃይል ለዉጥ እንደሚደረግ መንግስታትን እየመከሩ ይገኛሉ።

Solarsiedlung in Freiburg
ምስል፦ picture-alliance/dpa

የታዳሽ ኃይል ፍላጎት ሊጨምር መቻሉ

This browser does not support the audio element.

ታዳሽ ኃይል ምንጮች የሥራ እድሎችንለመፍጠርም ሆነ የአከባቢ ብክለትን ለመቀነስ ትልቅ ሚና እንደሚጫወቱባለሙያዎች ይናገራሉም። የዓለም አቀፍ የታዳሽ ኃይል ተቋም « IRENA» 82 የታዳሽ ኃይል ባለሙያዎችን ይዞ ለ42 ሀገሮች የኃይል አጠቃቀማቸዉንወደታዳሽ ኃይል እንዴት መቀየር እንደሚችሉእና ሌሎች ተጨማሪ አስፈላጊና ጠቃሚ ምክሮችን ለመለገስ ተዘጋጅቷል።

ባለሙያዎቹ የተለያዩ የታዳሽ ኃይል ምንጮችን፤ ወጪዎቻቸዉን፣ የሰዉ ኃይል ገበያ ላይ ሊኖር የሚችለዉን ተፅዕኖ፣ ብክለትን ለመቀነስ የሚጫወተውን ሚና፣ ከዛም አልፎ በመንግስትወይም ህብረተሰብ ግብይት ላይ ሊያመጣ የሚችለዉን ጥቅምና ጉዳት አጥንተዋል።

መርጋ ዮናስ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW