የትራምፕ ትዕዛዝ እና የሶማሌ ማህበረሰብ
ረቡዕ፣ ጥር 24 2009![Präsident Trump unterschreibt Dekret im Oval Office Weißes Haus](https://static.dw.com/image/37359358_800.webp)
ማስታወቂያ
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ካፀደቁት በኋላ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ተግባራዊ መሆን የጀመረው የጉዞ እገዳ ሰለባ ከሆኑት መካከል በአሜሪካን የሶማሌ ማህበረሰብ አባላት ይገኙበታል ። ትራምፕ እገዳውን ከመፈረማቸው ከሁለት ቀናት በፊት 90 ሶማሌዎች ከአሜሪካን እንዲባረሩ ተደርጓል ። ትዕዛዙ ከተላለፈ በኋላ ደግሞ የአሜሪካን ቋሚ የሥራ እና የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ሶማሊያውያን ለጉዞ በተለያዩ አውሮፕላን ጣቢያዎች በተገኙበት ወቅት መታሰራቸው እና መንገላታታቸውን ሶማሊያውያን ይናገራሉ ። ከትራምፕ ትዕዛዝ በኋላ በመወሰድ ላይ ባሉት በነዚህ እርምጃዎች አሜሪካ የሚኖሩ የሶማሌ ማህበረሰብ አባላት በፍርሃት መዋጣቸዉን የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን መክብብ ሸዋ ዘግቧል ።
መክብብ ሸዋ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ