የትራምፕ የአፍሪቃ መርሕ
ማክሰኞ፣ የካቲት 7 2009ማስታወቂያ
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ትናንት የደቡብ አፍሪቃ እና የናጄሪያ ፕሬዝደንቶችን በሥልክ አነጋግረዋል። ትራምፕ የፕሬዝደትነቱን ሥልጣን ከያዙ ወዲሕ የአፍሪቃ መሪዎችን ሲያነጋግሩ የትናንቱ የመጀመሪያቸዉ ነዉ። ንግግሩ ያተኮረበት ጉዳይ ግን በዉል አልታወቀም። የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ትራምፕ ከሳቸዉ በፊት የነበሩ የሐገራቸዉ መሪዎች ሥለ አፍሪቃ ባጠቃላይ፤ ሥለ ኢትዮጵያ በተለይ የሚከተሉትን መርሕ ሳይቀለብሱት አይቀርም። የዋሽግተን ዲ ሲ ወኪላችን መክብብ ሸዋ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
መክብብ ሸዋ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ