1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የበዓል ግብይት በአዲስ አበባ

እሑድ፣ ሚያዝያ 11 2012

በፋሲካ በዓል ዋዜማ በአዲስ አበባ አያት አደባባይ የተለያዩ የእርድ እንስሶች ለግብይት ቀርበው እና ገበያውም እንደወትሮው ሁሉ በተሟሟቀ ሁኔታ ሲከናወን ተስተውሏል። ይሁንና ግብይቱ ከእስከዛሬው የተቀዛቀዘ መሆኑን ሻጮችም ገዥዎችም ተናግረዋል።

Äthiopien | Ostern Markt in Addis Abeba
ምስል DW/S. Muchie

This browser does not support the audio element.

በዚሁ የገበያ ስፍራ በሬ፣ ፍየልና ዶሮን ጨምሮ በርከት ያሉ በጎች ለሽያጭ ቀርበዋል። ይሁንና ግብይቱ ከእስከዛሬው የተቀዛቀዘ መሆኑን ሻጮችም ገዥዎችም ተናግረዋል። በተለይ የበግ እና ፍየል ሽያጭ ላይ የዋጋ ጭማሪ መስተዋሉንና በአንጻሩ የበሬ እና ዶሮ ዋጋ በመጠኑም ቢሆን ቅናሽ እንዳለው የአዲስ አበባው ዘጋቢ ሰለሞን ሙጬ ያነጋገራቸው ሸማቾች ገልጸዋል። የግብይት ሂደቱ ግን የኮሮና ተኅዋሲ ከአንዱ ወደ ሌላው ለመተላለፍ አመቺ በሆነና በሚያጋልጥ ፣ የተሰጡ መመሪያዎች ሁሉ ችላ በተባሉበት አኳኋን ሲከናወን ተመልክተናል። ከቅዳሜ ረፋዱ ጀምሮ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ተዘዋውረን ባደረግነው የበዓል ዋዜማ ግብይት ትልልቅ የህንጻ የገበያ ማዕከላት ጭር ብለዋል።በድምጽ ማጉያ ይታገዙ የነበሩ የግብይት ጥሪዎች የሉም። የሰው ውር ውርም በእጅጉ ቀንሷል።

ምስል DW/S. Muchie

በ እርድ እንስሳት ይሞሉ የነበሩ ዋና ዋና መንገዶች ክፍት ሆነው ተስተውለዋል። በአጠቃላይ ግን በኮሮና ተህዋሲ ስጋት እና ይህንንም ተከትሎ መረርሽኙን ለመከላከል በወጡ የመንግሥት ከልካይ መመሪያ እና ደንቦች የተነሳ በከተማዋ የ2012 ዓም የትንሳኤ በዓል ግብይት ተቀዛቅዞ ተስተውሏል።
ሰለሞን ሙጩ 
ልደት አበበ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW