የትግራይ ክልል መንግስት ምርጫው መካሄድ አለበት አለ
ሰኞ፣ ሚያዝያ 19 2012ማስታወቂያ
የትግራይ ክልል መንግስት ዘንድሮ ሊካሄድ እቅድ ወጥቶለት የነበረው ሀገራዊ ምርጫ በወቅቱ መካሄድ ይገባዋል ሲል ገለጿል፡፡ የትግራይ ክልል ኮምኒኬሽን ቢሮ ሐላፊ ወይዘሮ ሊያ ካሳ ከዚህ ቀደምም ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ላይ ሆና ጭምር ምርጫ የማካሄድ ልምድ ነበራት ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል በትግራይ የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የፌደራሉ መንግስት ሀገራዊ ምርጫ የማያካሂድ ከሆነ የትግራይ ክልል መንግስት ለምርጫ ዝግጅት ማድረግ አለበት ሲሉ ጥሪ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ በበኩሉ ወቅታዊው የኮረና ቫይረስ ወረርሺኝ የምርጫ ዝግጅቱ መግታቱ ይገልፃል፡፡
ሚሊዮን ኃይለሥላሴ
ታምራት ዲንሳ
ነጋሽ መሐመድ