1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቻይናው ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር በኢትዮጵያ

ማክሰኞ፣ ጥር 2 2015

በቅርቡ ኃላፊነት የተሰጣቸው የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚነስትር ለሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተወያዩ። ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሺን ጋንግ ጋር ዛሬ መነጋገራቸውን ያስታወቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ «የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት አሁንም ጸንቶ ቀጥሏል» በማለት ጽፈዋል።

Chinesischer Außenminister Qin Gang in Äthiopien
ምስል Fana Broadcasting Corporate

ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተወያይተዋል

This browser does not support the audio element.

በቅርቡ ኃላፊነት የተሰጣቸው የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚነስትር ለሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተወያዩ። ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሺን ጋንግ ጋር ዛሬ መነጋገራቸውን ያስታወቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ «የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት አሁንም ጸንቶ ቀጥሏል» በማለት ጽፈዋል። ያደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ ከቻይና «በልማት የምትጋራውን ስልታዊ የጋራ ዓላማ፣ እንዲሁም አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ትብብርን አጉልቶ ያሳየ» ስለመሆኑም ገልፀዋል።

በቻይና ድጋፍ የተገነባው የአፍሪቃ የበሽታ መከላከል ማዕከል ዋና ጽሕፈት ቤት ከሰሞኑ እንደሚመረቅና አዲስ አበባ የገቡት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኑስትር በዚህ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።

የዩናይትድ ስቴትስና የቻይና ሽሚያ

የዓለም ሁለተኛው ግዙፉ ኢኮኖሚ ባለቤት የቻይና እና የአፍሪቃ አኅጉር ግንኙነት ሁለቱንም በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ እያደረገ ያለ ስለመሆኑ ይነገርለታል። 
ከ1990 ዎቹ መጨረሻ በተለይም ከ2000 ጀምሮ የቻይና አፍሪቃ የትብብር መድረክ መመስረትን ተከትሎ ቻይና እና አፍሪቃ በንግድ፣ በመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በብድር እና በሰው ኃይል ዘርፎች የላቀ ደረጃ እየደረሰ የመጣ ግንኙነት ስለመመስረታቸው የምርምር ሥራ ላይ የሚያተኩሩት ዶክተር ጌድዮን ጃለታ ተናግረዋል።

የቻይናው የባቡር መስመር ኩባንያ (CREC) የገነባው የቀላል ባቡር አገልግሎት በኢትዮጵያ፤ ፎቶ ከማኅደርምስል picture-alliance/dpaMarthe van der Wolf

ኃላፊነት በቅርቡ የተሰጣቸው የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚነስትር ለሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተው ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ተወያይተዋል። «ለምሳሌ ከ2015 ጀምሮ ቻይና 60 ቢሊዮን ዶላር ነው የሰጠችው ለአፍሪካ ሀገሮች» ብለዋል ባለሞያው። ይህም ገንዘብ ንግድን ለማቀላጠፍ፣ የኢንዱስትሪ መንደሮችን ለመገንባት፣ የግብርና ማዘመን ሥራዎችን ለማሳደግና ለሌሎችም የዋለ ስለመሆኑ ተገልጿል።

ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መነጋገራቸውን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ያደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ ከቻይና «በልማት የምትጋራውን ስልታዊ የጋራ ዓላማ፣ እንዲሁም አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ትብብርን አጉልቶ ያሳየ» ስለመሆኑም ገልፀዋል።

የአሜሪካ ቻይና እና ሩሲያ የአፍሪቃ ቀንድ የዲፕሎማሲ ጥረት አንድምታ
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዶክተር ቆስጠንጦኖስ በርኸ «ብዙ የአፍሪቃ ሀገሮች በዘመናቸው ያላዩት የመሰረተ ልማት እድገት ዕያሳዩ ነው» በማለት የቻይና አፍሪካ ግንኙነትን ደረጃ የት ላይነት ገልፀውታል።

ይህ ሁሉ እንዳለ ሆኖ ግን የሁለቱ አካላት ግንኙነት የላቀው የተጠቃሚነት ሚዛን ወደ ቻይና ያጋደለ ነው በሚል ይተቻል። ሀገራት በቻይና ምርት ከመጥለቅለቃቸው ባለፈ ለማይወጡት እዳ እየተዳረጉ ነው በሚል ጠንካራ መከራከሪያ ይነሳል። ዶክተር ጌድዮን ጃለታም ይሁን ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በርኸ ይህ እውነት የለውም ማለት እንደማይቻል ግን ጥቅሙ እንደሚያመዝን ገልፀዋል።

በቻይና መንግሥት ሙሉ የገንዘብ ድጋፍ የተገነባው የአፍሪቃ ኅብረት ዋና ጽ/ቤት በአዲስ አበባ ከተማ፤ ፎቶ ከማኅደርምስል AFP/Getty Images/J. Vaughan

ቻይና የአፍሪቃ ኅብረት ግዙፍ ግቢን ጨምሮ በርካታ ግንባታዎችን ለአፍሪካ አድርጋለች። አዲስ አበባ ላይ የተገነባው የአፍሪካ የበሽታ መከላከል ማዕከል ዋና ጽሕፈት ቤት ከሰሞኑ እንደሚመረቅና አዲስ አበባ የገቡት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኑስትር በዚህ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። 

ሰለሞን ሙጬ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

አዜብ ታደሰ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW