1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ከፌዴራል መንግስት ጋር ለመነጋገር ጥያቄ አቅርበዋል

ረቡዕ፣ ሰኔ 10 2012

ትናንት ወደ መቀሌ የተጓዘው የሀይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ስብስብ ከፌዴራል መንግስት ጋር ለመነጋገር ጥያቄ ማቅረቡን አስታወቀ። ጥያቄዎች ሁሉ በንግግርና በሰላም መፈታት አለባቸው በሚል ፣ በአሁኑ ወቅት በትግራይና በፌደራል መንግስት መካከል የሚስተዋለው ፍጥጫ ወደ ግጭት የማምራት አዝማሚያ በማሳየቱ ቅድሚያ እንደተሰጠው ተገልጿል

Ethiopian religious leaders met with the head of Tigray regional government Dr. Debretsion Gebremichael
ምስል፦ DW/M. Haileselassie

«ሽምግልና ላኪ እና ሽምግልና ተቀባይ የለም»

This browser does not support the audio element.

ትናንት ወደ መቀሌ የተጓዘው የሀይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ስብስብ ከፌዴራል መንግስት ጋር ለመነጋገር ጥያቄ ማቅረቡን አስታወቀ።
ሽማግሌዎቹ ግንቦት ወር ላይ ጥያቄዎች ሁሉ በንግግርና በሰላም መፈታት አለባቸው በሚል በስፋት ውይይት አድርገው እንደነበርና ፣ በአሁኑ ወቅት በትግራይና በፌደራል መንግስት መካከል የሚስተዋለው ፍጥጫ ወደ ግጭት የማምራት አዝማሚያ በማሳየቱ ቅድሚያ እንደተሰጠው ተገልጿል። ሽምግልና ላኪ እና ሽምግልና ተቀባይ በማይኖርበት ሀገር ችግር ውስጥ ከመግባቷ በፊት ለመታደግ በራሳቸው ተነሳሽነት እየተንቀሳቀሱ መሆኑንም የኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት አስታውቋል።

ሰለሞን ሙጬ

ታምራት ዲንሳ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW