1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቤንዚን ማደያ እጥረት የነዳጅ እጥረቱን አባብሶታል

ዓርብ፣ ጥር 5 2009

በያዝነዉ ሳምንት መግብያ የኢትዮጵያ ንግድ ሚኒስቴር በነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ይፋ ካደረገ በኋላ በተለይ የአዲስ አበባ ከተማ ላይ ብዙም ለዉጥ አለመታየቱን አንዳንድ ነዋሪዎች ገለፁ።

Mosambik Ponta do Ouro Tankstelle
ምስል imago/Anka Agency International

Ber. A.A. (Benzinpreis schießt in die Höhe) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.


የዋጋ ጭማሪዉ  በአንድ  ሊትር ቤንዚን ላይ አንድ ብር ከሰላሳ አንድ ሳንቲም ፤ ናፍጣ ላይ ደግሞ አንድ ብር ከዜሮ ሁለት ሳንቲም መጨመሩን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ በበኩላቸዉ በሀገሪቱ በሚገኙ ትልልቅ ከተሞች በተለይም ደግሞ በአዲስ አበባ በቂ የነዳጅ ማደያ ባለመኖሩ ለነዋሪዎች ምርቱን ለማዳረስ የሚደረገዉን ሥራ እንደሚያጓትተዉ ገልፀዋል።  በየከተማዉ የሚገኘዉ የቤንዚን ማድያ የከተሞችን እድገትና ከፍተኛ ቁጥር ተሽከርካሪዎችን ያላጤነ ነዉም ተብሎአል። ዝርዝሩን የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ልኮልናል።  


ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW