1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው በኅብረተሰቡ ላይ ያሳደረው ተጽእኖ በኢትዮጵያ፦ ውይይት

እሑድ፣ ጥር 18 2017

በኢትዮጵያ የኤኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ይፋ ከሆነበት ጊዜ አንስቶ መንግሥት ድጎማ ያደርግባቸው የነበሩ አገልግሎቶች ላይ በሒደት ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ተከስቷል ። መንግሥት የአዲስ አበባ የነዳጅ ምርቶች ግብይት ጉልኅ የመሸጫ ዋጋን ይፋ ካደረገበት ጊዜ አንስቶ ነዋሪዎች የዕለት ተዕለት ኑሯቸውን ለመግፋት ይበልጥ እጅግ መቸገራቸውን እየተናገሩ ነው ።

Äthiopien | Tigray | Treibstoff Versorgungsengpässe
ምስል፦ Million Haileselassie/DW

የነዳጅ ዋጋ ያስከተለው ጫና ኅብረተሰቡን እጅግ አማሯል

This browser does not support the audio element.

በኢትዮጵያ የኤኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ይፋ ከሆነበት ጊዜ አንስቶ መንግሥት ድጎማ ያደርግባቸው የነበሩ አገልግሎቶች ላይ በሒደት ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ተከስቷል  ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አግልግሎት፣ የኢትዮ ቴሌኮም፣ የውኃ እና ፍሳሽ አገልግሎቶች የክፍያ ተመን ቀደም ሲል ጨምረዋል ። 

መንግሥት ማክሰኞ ታኅሣሥ 29 ቀን፣ 2017 ዓ.ም ደግሞ የአዲስ አበባ የነዳጅ ምርቶች ግብይት ጉልኅ የመሸጫ ዋጋን  ይፋ ካደረገበት ጊዜ አንስቶ ነዋሪዎች ወትሮም ያንገዳግዳቸው የነበረ የዕለት ተዕለት ኑሯቸውን ለመግፋት እጅግ መቸገራቸውን እየተናገሩ ነው ።  በተለያዩ ቦታዎችም ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት ተከስቷል ።

በመንግሥት መዋቅር ስር ያሉ ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በመቀናጀት የነዳጅ አቅርቦቱን ይሸሽጋሉ ብሎም በጥቁር ገበያ በከፍተኛ ዋጋ ይቸበችባሉ የሚሉ ቅሬታዎች እያስተጋቡ ነው ። እጥረቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ ለአብነት፦  ከሰሞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተሽከርካሪዎች መቆማቸው  ተገልጧል ።

ያም ብቻ አይደለም፥ የክልሉ ነዋሪዎች በባሕላዊ መንገድ በፈረስ በበቅሎ፣ በአህያ እና በጋሪ የመጓጓዣ አገልግሎት መጀመራቸውን መጥቀሳቸው እጅግ አስደምሟል ። «የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው በኅብረተሰቡ ላይ ያሳደረው ተጽእኖ በኢትዮጵያ» የዛሬው እንወያይ መሰናዶ ዐቢይ ትኩረት ነው ። በውይይቱ 4 እንግዶች ተሳታፊ ናቸው ።

1-ኤሚሬተስ ፕሮፌሰር ዳንኤል ተፈራ

2-ዶ/ር አብዱልመናን መሃመድ፤ የምጣኔ ሐብት ባለሙያ

3-አቶ ክቡር ገና፤ የፓን አፍሪካ የንግድ እና የኢንድስትሪ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር

4- አቶ ዓማንይሁን ረዳ፦ የንግድ እና ኤኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ ናቸው ተወያዮች ።

በነዳጅ እጥረት በርካታ ተሽከርካሪዎች በሰልፍ ተደርድረው። ፎቶ፦ ከማኅደርምስል፦ Shewangizaw Wogayehu/DW

ጉልኅ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ላይ በሚያወሳው በዚህ ውይይት መንግስት ተሳታፊ እንዲመድብ ለጠቅላይ ሚንሥትር ጽ/ቤት ይፋዊ የኢሜል ግብዣ ብንልክም ውይይቱን እስካደረግንበት ጊዜ ድረስ ምላሽ አላገኘንም ።

ሙሉውን ውይይት በድምፅ ማእቀፉ ማድመጥ ይቻላል ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW