1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የኢድ አል አደሀ መልዕክት

ሰኞ፣ ሐምሌ 12 2013

1442ኛው ሂጅራ የኢድ አል አደሀ በዓልን ስናከበር በተለያዩ ምክንያቶች ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉና የተቸገሩ ወገኖችን በማገዝ መሆን እንደሚገባ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አሳሰበ። አገራችን የገጠማትን የውስጥና የውጭ ጫና በመተባበር ልናስወግደው ገባልም ብሏል ምክር ቤቱ፡፡ 

Äthiopien Bahir Dar | Pressekonferenz
ምስል፦ Alemnew Mekonnen/DW

የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የኢድ አል አደሀ መልዕክት

This browser does not support the audio element.

የዘንድሮውን የኢድ አል አደሀ በዓል ምክንያት በማድረግ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡ የምክር ቤቱ ፕረዚደንት ሸክ ሰኢድ መሐመድ ዛሬ በጽ/ቤታቸው ግቢ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በዓሉ የሰላምና የፍቅር፣ የመረዳዳት እንዲሆንም ተመኝተዋል፡፡ 
በአማራ ክልልና በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በነበሩ ግጭቶች የተፈናቀሉ በርካታ ዜጎች መኖራቸውን አስታውሰው፣ በዓሉን ስናከብር እነኝህን ወገኖች መርዳት ያስፈልጋል፣ በፈጣሪ ዘንድም ዋጋ አለው ብለዋል፡፡ 
ብዙ ተግዳሮቶች ያሉበት ወቅት ቢሆንም የዚህን ዓመት ኢድ አል አደሀ ልዩ ያደርገዋል ያሉትን ሁኔታም ጠቁመዋል፡፡ 
ያጋጠሙንን ችግሮች ለመፍታት በሁሉም መስክ ትብብራችንን ማድረግ፣ በተለይ ደግሞ ወደ ፈጣሪ ፊታችን በማዞር መፀለይና መለመን አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ሸክ ሰኢድ አመልክተዋል፡፡ 
በእለቱ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አባላትና ሰራተኞች በምክር ቤቱ ግቢ የችግኝ ተከላ ስነስርዓት አካሂደዋል፣ እንደዚሁም መስማት ለተሳናቸው ወገኖች የዘይትና የዱቄት እርዳታ ተደርጓል፡፡ 

ዓለምነው መኮንን 

ኂሩት መለሰ
  

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW