1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአማራ ክልል የብሔራዊ ምክክር ተሳታፊዎች አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ አስረከቡ

ዓለምነው መኮንን
ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 4 2017

በአማራ ክልል ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 4 ቀን 2017 የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ ተከናውኗል። በሒደቱ ከክልልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተወከሉ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ በሚካሔደው ብሔራዊ ምክክር ሊቀርቡ ይገባል ያሏቸውን ርዕሰ ጉዳዮች በመለየት ለኮሚሽኑ ዛሬ አስረክበዋል፡፡

የአማራ ክልል የብሔራዊ ምክክር ተሳታፊዎች
የአማራ ክልል የብሔራዊ ምክክር ተሳታፊዎች አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ አስረከቡምስል፦ Alemnew Mekonnen/DW

የአማራ ክልል የብሔራዊ ምክክር ተሳታፊዎች አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ አስረከቡ

This browser does not support the audio element.

ሠሞኑን በክልሉ ሲካሄድ የነበርው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደትና በአዲስ አበባ ለሚካሄደው አገር አቀፍ ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችም ተመርጠዋል፡፡ ከአዊ ብሔረስብ አስተዳደር ተወክለው የመጡ አንድ አስተያየት ሰጪ ሁሉም ሀሳቡን አውጥቶ መስጠቱን ጠቁመው የተነሱ ሀሳቦች በመንግሥት ተቀባይነት ካላቸው  ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በብሔራዊ ምክክር እንዲሳተፉ ተጨማሪ ጥሪ ቀረበ

ሌላው አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው የማያግባቡን ነገሮች መፍትሔ አግኝተው ተግባብተን መኖር የሚያስችል ውይይት ማድረግ እንደተቻለ ነው ለዶይቼ ቬሌ አስተያየታቸውን የሰጡት፡፡

አዲስ አበባ ላይ በሚደረገው አገራዊ ምክክርም የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የተሻለ መግባባት እንደሚፈጠር ገልጠዋል፡፡

አንድ አስተያየት ሰጪ ሁሉም ሀሳቡን አውጥቶ መስጠቱን ጠቁመው የተነሱ ሀሳቦች በመንግሥት ተቀባይነት ካላቸው  ውጤት ያመጣሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ምስል፦ Alemnew Mekonnen/DW

በመነጋገር የማይፈታ ችግር እንደሌለ የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ በሂደቱም የተሻለ ነገር ይመጣል ብለዋል፡፡ የምክክር መድረኩ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮንሚሽን ኮሚሽነር መላኩ ወልደማሪያም በአማራ ክልል የተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብና በአዲስ አበባ ጉባኤ የሚወከሉ ተሳታፊዎችን የመምረጡ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን ገልጠዋል። 

የአጀንዳ ማሰባሰብ በአማራ ክልል

በአማራ ክልል ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዘያ 4/2017 ዓም  የተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮች ተመርጠዋል፡፡ በሁለት ምዕራፍ ሲካሄድ በቆየው የአማራ ክልል የምክክር ሂደት ከ6ሺህ በላይ ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡
 
ዓለምነው መኮንን

እሸቴ በቀለ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW