1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከመንግስት ጋር «አልተደራደርኩም» አለ (የታረመ)

ነጋሽ መሐመድ
ሐሙስ፣ ጥር 22 2017

አቶ እስክንድር ነጋ የሚመሩት የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት በዉጪ ሸምጋዮች አማካይነት ከመንግሥት ጋር ድርድር ጀምሯል የሚሉ ዘገቦች ሰሞኑን ተሰራጭተዉ ነበር።የግንባሩ መሪ እስክንድር ነጋ ዛሬ እንዳሉት ግን ድርጅታዉ ድርድር አልጀመረም

አቶ እስክንድር ነጋ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መሪ።ድርጅታቸዉ ከአፍሪቃ ሕብረት፣ከኢጋድ፣ ከአዉሮጳ ሕብረትና ከዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት ጋር ተወያይቷል
አቶ እስክንድር ነጋ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መሪ።የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከመንግስት ጋር «አልተደራደርኩም» አለ።አቶ አስክንድር እንደሚሉት ድርጅታቸዉ ከመንግሥት ጋር አልተደራደረም።ምስል፦ picture alliance/AP Images

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከመንግስት ጋር «አልተደራደርኩም» አለ (የታረመ)

This browser does not support the audio element.

 

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር አልተደራደርኩም አለ።አቶ እስክንድር ነጋ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት በዉጪ ሸምጋዮች አማካይነት ከመንግሥት ጋር ድርድር ጀምሯል የሚሉ ዘገቦች ሰሞኑን ተሰራጭተዉ ነበር።የድርጅቱ መሪ እስክንድር ነጋ ዛሬ እንዳሉት ግን ድርጅታዉ ድርድር አልጀመረም።ይሁንና የድርጅቱ መሪዎች ሥለ ድርጅቱ ዓላማ፣ በአማራ ክልል ይፈፃማሉ ሥለሚባሉ የጦር ወንጀሎችና ሥለ ሠብአዊ ርዳታ አቅርቦት ከዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ተወካዮች ጋር መወያየታቸዉን አቶ እስክንድር አስታዉቀዋል።

ነጋሽ መሐመድ 

ፀሐይ ጫኔ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW