1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ትራምፕ ሊከሰሱ ነው

ማክሰኞ፣ ጥር 4 2013

የምክር ቤቱ አባላት በክሱ ላይ ረቡዕ ድምጻቸውን ይሰጣሉ ተብሏል።ባለ አራት ገጹ የምክር ቤቱ ደብዳቤ ፕሬዝዳንት ትራምፕን ፣የዩናይትድ ስቴትስን ደህንነትና የመንግሥት ተቋማት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን ለአደጋ በማጋለጥና ሰላማዊ ሽግግርን በማወክ ይከሳል።ትራምፕ ለሐገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት ዴሞክራሲና ሕገ መንግሥት አስጊ መሆናቸው ተጠቅሷል።

USA Washington DC Capitol Ausschreitungen
ምስል DW

ትራምፕ ሊከሰሱ ነው

This browser does not support the audio element.

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤቶች መቀመጫ ካፒቶል ሂል አመጽ በማስነሳት ሊከሰሱ ነው። የአሜሪካን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ክሱን ያቀርባል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። በአሶስየትድ ፕሬስ ዘገባ መሠረት የምክር ቤቱ አባላት በክሱ ላይ ረቡዕ ድምጻቸውን ይሰጣሉ ተብሏል። ባለ አራት ገጹ የምክር ቤቱ ደብዳቤ ፕሬዝዳንት ትራምፕን ፣ የዩናይትድ ስቴትስን ደህንነትና የመንግሥት ተቋማት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን ለአደጋ በማጋለጥና ሰላማዊ ሽግግርን በማወክ ይከሳል። ትራምፕ በስልጣን ላይ እንዲቆዩ ከተደረገ አሁንም ለሐገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት ዴሞክራሲ እና ሕገ መንግሥት አስጊ መሆናቸው በደብዳቤው ተጠቅሷል። በትራምፕ ላይ ይመሰረታል ስለሚባለው ክስ የዋሽንግተን ዲሲውን ዘጋቢያችንን አነጋግረናቸዋል።


አበበ ፈለቀ
ኂሩት መለሰ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW