1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጉዞ ማስጠንቀቂያ

ረቡዕ፣ ሰኔ 7 2009

በአሁኑ ማስጠንቀቂያ የአሜሪካን ዜጎች እንዳይሄዱ የተከለከሉት ጎንደር እና ባህርዳር ነው። ሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ትናንት ባወጣው መግለጫ የአሜሪካን ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ሲጓዙ አደጋ ሊያጋጥማቸው እንደሚችል አስጠንቅቋል።

US-Außenministerium
ምስል AFP/Getty Images/J. Richards

Beri.Wash(US travel warning to Ethiopia) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

 

ዩናይትድ ስቴትስ ከዚህ ቀደም ለዜጎቿ ያወጣችውን የኢትዮጵያ ጉዞ ማስጠንቀቂያ አራዘመች። የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ትናንት ባወጣው መግለጫ የአሜሪካን ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ሲጓዙ አደጋ ሊያጋጥማቸው እንደሚችል አስጠንቅቋል። በአሁኑ ማስጠንቀቂያ የአሜሪካን ዜጎች እንዳይሄዱ የተከለከሉት ጎንደር እና ባህርዳር ነው። እንደ መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ መንግሥት በየጊዜው የስልክ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ስለሚዘጋ በኢትዮጵያ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ለሀገሩ ዜጎች ሊደርስ እና የምክር አገልግሎት ሊሰጥ አልቻለም ። ስለ ተራዘመው ማስጠንቀቂያ የአሜሬካን ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪቃ ክፍል ቃል አቀባይን ያነጋገረው የዋሽንግተን ዲሲው ዘጋቢያችን መክብብ ሸዋ ዝርዝር ዘገባ አለው።
መክብብ ሸዋ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW