የአሜሪካ መንግሥት ነጻ የትምህርት ዕድል ለሴት ተማሪዎች
ዓርብ፣ ጥቅምት 12 2003ማስታወቂያ
አሜሪካ በኤምባሲዋ አማካኝነት ለ1000 ኢትዮዽያውያን ሴቶች በሀገር ውስጥ የሚደረግ ነጻ የትምህርት ዕድል እንደሰጠ አስታውቋል። ይህ ዕድል የተሰጠው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተለያዩ ችግሮች የተነሳ ከሚፈልጉበት ጥሩ ደረጃ ማድረስ ላልቻሉ ሴት ተማሪዎች እንደሆነ ተገልጿል። የአሜሪካ የግብረሰናይ ድርጅት ዩኤ ኤይድ ለዚህ ተግባር የ16ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።ፍሪ አዲስ በተሰኘ ሀገር በቀል ድርጅት አማካኝነት ስራው እንደሚከናወንም ታውቋል። ጌታቸው ተድላ ከአዲስ አበባ ዘገባ አለው።
መሳይ መኮንን
ተክሌ የኋላ