የአሜሪካ ረቂቅ ሕግጋትና ኢትዮጵያዉያን
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 4 2014
ማስታወቂያ
ለዩንይትድ ስቴትስ ምክር ቤቶች የቀረቡት ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ረቂቅ ሕግጋት እንዳይፀድቁ እዚያዉ ዩናይትድ ስቴትስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንና ኢትዮጵያዉያን አሜሪካዉያን ምሁራን ጠየቁ።የዩናይትድ ስቴትስ ሕግ-መምሪያና ሕግ-መወሰኛ ምክር ቤቶች አባላት ያረቀቋቸዉ HR 6600 እና S 3199 ሕግጋት ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረጉ ግጭቶች፣ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችና በደሎችን ለማስቆም፣ ሠላምና ዴሞክራሲን ለማስፈን የሚረዱ፣ጥፋተኞችን የሚቀጡ ናቸዉ።130 የሚሆኑት ምሁራን ለሁለቱ ምክር ቤቶች በፃፉት ደብዳቤ እንዳሉት ግን ረቂቆቹ ኢትዮጵያን የሚጎዱ፣ የአሜሪካና የኢትዮጵያን ወዳጅነትንም የሚያበላሹ ናቸዉ።
ታሪኩ ኃይሉ
ነጋሽ መሐመድ
ማንተጋፍቶት ስለሺ