ኢትዮጵያና ኤርትራን ያወገዘው የአሜሪካን መግለጫ
ሰኞ፣ ግንቦት 9 2013![USA, Washington I Außenministerium der Vereinigten Staaten I State Department](https://static.dw.com/image/55102926_800.webp)
ማስታወቂያ
የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ላይ የሚያራምደውን የውጪ ግንኙነት ፖሊሲ በግልፅ አለማስቀመጡ ኢትዮጵያን ለተደጋጋሚ ተፅዕኖ እየዳረጋት መሆኑን ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው የሰላም ሚኒስቴር ባለሥልጣን ገለፁ።ባለፈው ቅዳሜ የአሜሪካን መንግሥት ባወጣው «የኤርትራና የኢትዮጵያን መንግሥታት በሚያወግዝ መግለጫ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት ባለሥልጣኑ ፣ ስለ ኢትዮጵያ የሚወጡ የተሳሳቱ መረጃዎችና የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ያልተጣራ የመረጃ ስርጭት እውነትን እያናጋ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንድታሳርፍ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ገልጸዋል።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኤርትራ እና የኢትዮጵያ መንግሥታት የሚወገዝ እና ተቀባይነት የሌለው ያለውንና በትግራይ እየተፈፀመ ነው ያለውን ድርጊት ለማስቆም የሁለቱ ሀገራት መንግሥታት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቋል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ