1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያና ኤርትራን ያወገዘው የአሜሪካን መግለጫ

ሰኞ፣ ግንቦት 9 2013

ባለፈው ቅዳሜ የአሜሪካን መንግሥት ባወጣው «የኤርትራና የኢትዮጵያን መንግሥታት በሚያወግዝ መግለጫ ላይ  አስተያየታቸውን የሰጡት ባለሥልጣኑ፣ስለ ኢትዮጵያ የሚወጡ የተሳሳቱ መረጃዎችና የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ያልተጣራ የመረጃ ስርጭት እውነትን እያናጋ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንድታሳርፍ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ገልጸዋል።

USA, Washington I Außenministerium der Vereinigten Staaten I State Department
ምስል Alastair Pike/AFP/Getty Images

ኢትዮጵያና ኤርትራን ያወገዘው የአሜሪካን መግለጫ

This browser does not support the audio element.

የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ላይ የሚያራምደውን የውጪ ግንኙነት ፖሊሲ በግልፅ አለማስቀመጡ ኢትዮጵያን ለተደጋጋሚ ተፅዕኖ እየዳረጋት መሆኑን ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው የሰላም ሚኒስቴር ባለሥልጣን ገለፁ።ባለፈው ቅዳሜ የአሜሪካን መንግሥት ባወጣው «የኤርትራና የኢትዮጵያን መንግሥታት በሚያወግዝ መግለጫ ላይ  አስተያየታቸውን የሰጡት ባለሥልጣኑ ፣ ስለ ኢትዮጵያ የሚወጡ የተሳሳቱ መረጃዎችና የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ያልተጣራ የመረጃ ስርጭት እውነትን እያናጋ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንድታሳርፍ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ገልጸዋል።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኤርትራ እና የኢትዮጵያ መንግሥታት የሚወገዝ እና ተቀባይነት የሌለው ያለውንና በትግራይ እየተፈፀመ ነው ያለውን ድርጊት ለማስቆም የሁለቱ ሀገራት መንግሥታት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቋል። 


ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW