የአሜሪካ የማዕቀብ እቅድ ሁለቱንም ሃገሮች ይጎዳል መባሉ
ሐሙስ፣ ጥቅምት 4 2014ማስታወቂያ
ዩናይትድስቴትስ በኢትዮጵያ ላይ የምጣኔ ሃብት ማዕቀብ ለመጣል እያጤነች መኾኗን ማስታወቋ የሁለቱን ሃገሮች ስትራቴጂካዊ ግንኙነትና ጠቀሜታ የሚጎዳ መሆኑን በአሜሪካ ዶይቸ ቨለ ያነጋገራቸው የሲቪክ ድርጅቶች ተወካዮች አስታወቁ። የአሜሪካ ኢትዮጵያውያን ሕዝብ ጉዳዮች አስፈፃሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር አቶ መስፍን ተገኑ እንደገለፁት የዩናይትድስቴትስ አካሄድ የሁለቱን ሃገሮች ወዳጅነትና ጥቅም የሚጎዳ ነው። የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ድምፅ ንቅናቄ ተወካይ ወይዘሮ ሜሮን አሐዱ በበኩላቸው የኢትዮጵያና አሜሪካን የጋራ ጥቅም ይጎዳል ያሉትን ጫና ለመከላከል የሚያስችል የተጠናከረ የሕዝብ ዲኘሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ይካሄዳል ብለዋል።
ታሪኩ ኃይሉ
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ