የአሜሪካ ጥቁሮች ቤተ-መዘክር
ዓርብ፣ መስከረም 20 2009ማስታወቂያ
የዩናይትድ ስቴትስ ጥቁር ዜጎችን ታሪክ፤ ባሕል፤ በባርነት ዘመን ይፈፀምባቸዉ የነበረዉ ግፍና የአሁን አኗኗራቸዉ የሚታወስበት ብሔራዊ ቤተ-መዘክር ወይም ሙዚየም ዋሽግተን ዲሲ ዉስጥ ሰሞኑን ተመርቆ ተከፈተ። በመክፈቻዉ ሥነ-ሥርዓት ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ባራክ ኦቦማ፤ የቀድሞ ፕሬዝደንቶች፤ ፖለቲከኞችና ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል። ቤተ መዘክሩን ለማሠራት ከግማሽ ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ሆኖበታል። የዋሽግተን ዲ ሲዉ ወኪላችን መክብብ ሸዋ ዝርዝር ዘገባ አለዉ