1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ«አሜን ኢትዮጵያ» ድርጅት ጉባዔ 

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 4 2009

በተለያዩ የአውሮጳ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የመሰረቱት አሜን ኢትዮጵያ የተባለው ድርጅት ሰሞኑን በአዲስ አበባ ጉባዔ አካሄደ። ይኸው በኔዘርላንድስ የተቋቋመው ድርጅት በጉባዔው ያጎላው ዋና ነጥብ የመደማመጥ እና የመግባባት ባህልን በማዳበር ለልዩነቶች እና ለግጭቶች መፍትሔ ማስገኘት የሚለውን ነው።

NO FLASH Symbolbild Frieden
ምስል picture alliance/Arco Images GmbH

Ber. AA('Amen Ethiopia' über Konfliktmanagement & Friedensförderung) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

በጉባዔው የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚደንት የመቶ አለቃ ግርማ ወልደጊዮርጊስ እና ስለሰላም ጥናት እና ምርምር ያደረጉ ምሁራን ተገኝተዋል። በኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት እና ማህበራት ኤጀንሲ ተመዝግቦ የሚሰራው ይኸው ድርጅት ጉባዔውን ያካሄደው የቀድሞው ፕሬዚደንት የመቶ አለቃ ግርማ ወልደጊዮርጊስ ለሰላም ስብሰባዎች በግቢያቸው ባሰሩት አዳራሽ ነበር። 

ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW