1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 የአምባሳደር ዮአኺም ሽሚት ሞት

ማክሰኞ፣ ሰኔ 6 2009

አምባሳደር ሽሚት በተለይ ከወጣቶች ጋር ስፖርትን በመሳሰሉ መስኮች በመገናኘት ወጣቶችን የሚደግፉና የሚያበረታቱ፤ የኢትዮጵያና የጀርመንን ግንኙነት ለማጠናከር አብክረዉ የጣሩ አምባሳደርም ነበሩ

Äthiopien Joachim Schmidt
ምስል Deutsche Botschaft Äthiopien

(Beri.AA) Tod von Deutscher Botschafter in AA - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ዮአኺም ሽሚት በማረፋቸዉ በቅርብ የሚያዉቋቸዉ ሐዘናቸዉን እየገለፁ ነዉ።አምባሳደር ሽሚት በጀርመን መንግሥትና ድርጅቶች የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን በየአካባቢዉ እየተዘዋወሩ በመጎብኘት፤ ለሕዝቡ የሚሰጡትን አገልግሎት በማበረታትና ከየማሕበረሰቡ ጋር በመወያየት የታወቁ ዲፕሎማት ነበሩ።አምባሳደር ሽሚት በተለይ ከወጣቶች ጋር ስፖርትን በመሳሰሉ መስኮች በመገናኘት ወጣቶችን የሚደግፉና የሚያበረታቱ፤ የኢትዮጵያና የጀርመንን ግንኙነት ለማጠናከር አብክረዉ የጣሩ አምባሳደርም ነበሩ።ሽሚት እንደ ጎርጎሪያኑ አቆጣጠር በ2014 በኢትዮጵያ እና በአፍሪቃ ሕብረት የጀርመን አምባሳደር ሆነዉ ከመሾማቸዉ በፊት በቦስኒያ ሄርሶ ጎቪና እና በሰርቢያ የጀርመን አምባሳደር ሆነዉ አገልግለዋል።በሞታቸዉ የተነገረዉ ትናንት ነዉ።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ


 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW