1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ፖለቲካሰሜን አሜሪካ

የአምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ኃላፊነት የመልቀቅ ጉዳይ

ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 8 2014

ከኃላፊነታቸው ይለቃሉ የተባሉት በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ ልዑክ ዴቪድ ሳተርፊልድ በሱዳን ችግር እንደገቸማቸው በአትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል አባል አቶ ገብርኤል ንጋቱ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ በአምባሳደርነት የሠሩት ዴቪድ ሺን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ልዩ ልዑኩን "በአጭር ጊዜ ለመተካት" እንደሚቸግረው ተናግረዋል።

Libanon - US David Satterfield mit Libanesischem Außenminister Bassil
ምስል፦ picture alliance/AP Photo/B. Hussein

የአምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ኃላፊነት የመልቀቅ ጉዳይ

This browser does not support the audio element.

በአፍሪካ ቀንድ የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ልዑክ ዴቪድ ሳተርፊልድ ሥልጣኑን በያዙ በአጭር ጊዜ ሥልጣን እንደሚለቁ መገለጹ ያልተለመደ ውሳኔ መሆኑን አንድ የቀድሞ የዩናይትድስቴትስ ዲኘሎማት ገለጹ።

በኢትዮጵያና በቡርኪናፋሶ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሳደር ዴቪድ ሺን በተለይ ለዶይቸ ቨለ እንዳሉት፣ ልዩ ልዑኩ ለምን ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ የሚያውቁት ነገር ባይኖርም ዕርምጃው ባልተለመደ ሁኔታ በአጭር ጊዜ የተወሰደ ነው።

በዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የጥናት ማዕከል አትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል አባል አቶ ገብርኤል ንጋቱ በበኩላቸው ልዩ ልዑኩ በሱዳን በሚያደርጉት የሰላም ጥረት ችግር ይግጠማቸው እንጂ ስራ እንደሚለቁ ግን አለመናገራቸውን ገልጸዋል።

ታሪኩ ኃይሉ 
እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW