1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአርያና ግራንዲ ዝግጅት

ሰኞ፣ ግንቦት 28 2009

የ23 ዓመትዋ ወጣት አርያና በማንቼስተር ከተማ ባዘጋጀችው በዚሁ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ሌሎች እውቅ ከያንያንም ተካፍለዋል።

Benefizkonzert nach Anschlag in Manchester Ariana Grande
ምስል Picture alliance/AP Photo/D. Hogan

Beri London(Arianna Grande's one love concert) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የብሪታንያ ፖሊስ ባለፈው ቅዳሜ ምሽት ሰባት ሰዎች በተገደሉበት እና 48 ሰዎች ከቆሰሉበት ከለንደን ብሪጁ ጥቃት ጋር  ግንኙነት አላቸው ብሎ የጠረጠራቸውን ማደን እና ማሰሩን ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። የታሰሩት ቁጥር 12 ደርሷል። በብሪታንያ በሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለሦስተኛ ጊዜ ለተፈፀመው ለዚሁ ጥቃት ራሱን እስላማዊ መንግሥት ብሎ የሚጠራው ቡድን ሃላፊነቱን ወስዷል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎች ማደኑን በቀጠለበት በትናንትናው እለት በብሪታንያዋ ሰሜናዊ ከተማ ማንቼስተር ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደው የአርያና ግራንዲ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ በተጣለው ጥቃት ለሞቱት እና ለተጎዱ ቤተሰቦች መርጃ የተዘጋጀው የሙዚቃ ትርዒት ተካሂዷል። የ23 ዓመትዋ ወጣት አርያና በማንቼስተር ከተማ ባዘጋጀችው በዚሁ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ሌሎች እውቅ ከያንያንም ተካፍለዋል። የለንደኑ ወኪላችን ድልነሳው ጉጌታነህ ዝዝርሩን ልኮልናል ።

ድልነሳው ጉታነህ 

ኂሩት መለሠ

ሸዋዬ ለገሠ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW