1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአሸንዳ በዓል አከባበር በመቀሌ

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 16 2015

ከ2011 ዓመተምህረት በኃላ በተለያዩ ምክንያቶች የቀድሞ ድምቀቱ አጥቶ እና ሲስተጓገል የቆየው በትግራይ ሴቶች ዘንድ በየዓመቱ በድምቀት የሚከበረው የአሸንዳ በዓል ከአራት ዓመታት በኃላ ዘንድሮ በድምቀት እየተከበረ ነው

የትግራይ ልጃገረዶች በየዓመቱ  የሚከበሩት የአሸንዳ በዓል
የትግራይ ልጃገረዶች በየዓመቱ የሚከበሩት የአሸንዳ በዓል ዘንድሮ ከጦርነቱ በኋላ በድምቀት ተከብሯል ምስል Million Hailesilassie /DW

በትግራይ የአሸንዳ በዓል ከአራት ዓመታት በኃላ ዘንድሮ በድምቀት እየተከበረ ነው።

This browser does not support the audio element.

የትግራይ ልጃገረዶች በየዓመቱ  የሚከበሩት የአሸንዳ በዓል ከጦርነቱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በድምቀት እየተከበረ ነዉ። በዓሉ መጀመርያ ላይ በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ቀጥሎም በ2013 በተጀመረዉ  ጦርነት ምክንያት የቀድሞ ድምቀቱ አጥቶ ነበር። የዘንድሮው የአሸንዳ በዓል በተለይም በመቐለ ከተማ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶች በተገኙበት እየተከበረ ነዉ።የመቀሌዉ ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለ ስላሴ እንደዘገበዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስአበባ ወደ መቐለ በቀን ከ12 በላይ በረራዎች እያደረገ ነዉ። ሆቴሎች ሞልተዋል፤ ጭር ብለው የነበሩ መንገዶች በተሽከርካሪ እና በሰው ተሞልተዋልም።

የትግራይ ልጃገረዶች ዘንድሮ ከጦርነቱ በኋላ የአሸንዳ በዓልን በድምቀት አክብረዋልምስል Million Hailesilassie /DW

ከ2011 ዓመተምህረት በኃላ በተለያዩ ምክንያቶች የቀድሞ ድምቀቱ አጥቶ እና ሲስተጓገል የቆየው በትግራይ ሴቶች ዘንድ በየዓመቱ በድምቀት የሚከበረው የአሸንዳ በዓል ከአራት ዓመታት በኃላ ዘንድሮ በድምቀት እየተከበረ ነው።ከፍልሰታ ፆም በኋላ ከነሐሴ 16 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት የሚከበረው ይህ በዓል በሁሉም የትግራይ አካባቢዎች ጨምሮ በአማራ ክልል እንዲሁ በሴት ልጃገረዶች በተለያየ ባህላዊ ይዘት የሚከበር ነው።

የትግራይ ልጃገረዶች ዘንድሮ ከጦርነቱ በኋላ የአሸንዳ በዓልን በድምቀት አክብረዋልምስል Million Hailesilassie /DW

 

መጀመርያ ላይ በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ቀጥሎም በ2013 ዓመተምህረት በተከሰተው ጦርነት ምክንያት አሸንዳ የቀድሞ ድምቀቱ አጥቶ ቆይቷል። የዘንድሮው የአሸንዳ በዓል በተለይም በመቐለ ካለፊት ዓመታት የተለየ ድባብ ይዟል። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶች ለበዓሉ (ካርኒቫል) ወደ መቐለ መጥቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀን ከ12 በላይ በረራዎች ከአዲስአበባ ወደ መቐለ እያደረገ ሲሆይ ሆቴሎች ሞልተዋል፣ ጭር ብለው የነበሩ መንገዶች በተሽከርካሪ እና ሰው ተሞልተው ይታያሉ።

ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW