1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአቶ አሰፋ ጫቦ ኅልፈት

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 17 2009

በንጉሠ ነገሥት ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት ለጥያቄ እና መልስ ውድድር  ወደ አሜሪካን ሀገር ተልከው ያሸነፉ እና ከንጉሡም የወርቅ የእጅ ሰአት የተሸለሙት ዕውቁ ፖለቲከኛ አቶ አሰፋ ጫቦ አረፉ።

Explosion Behindertenwerkstatt Titisee Neustadt
ምስል Christof Stache/AFP/Getty Images

Ber. DC (Assefa Chamo passed away) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

በንጉሠ ነገሥት ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት ለጥያቄ እና መልስ ውድድር  ወደ አሜሪካን ሀገር ተልከው ያሸነፉ እና ከንጉሡም የወርቅ የእጅ ሰአት የተሸለሙት ዕውቁ ፖለቲከኛ አቶ አሰፋ ጫቦ አረፉ። ጸሐፊ፣ የሕግ ባለሞያ እና የምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ አሰፋ ጫቦ በደርግ ዘመነ-መንግሥት ለ10 ዓመት ከመንፈቅ ታስረው እንደተፈቱ  በቅርብ የሚያውቋቸው ይናገራሉ። በኢሕአዴግ አገዛዝ ደግሞ ከሀገር ተሰደው ሕይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ነዋሪነታቸውን በአሜሪካ አድርገው ነበር።  ከረዥም ዓመታት የጽሞና ጊዜ በኋላ ላለፉት ሁለት ዓመታት በማኅበራዊ የመገናኛ አውታሮች በተለይም በፌስቡክ ብቅ ብለው በተከታታይ ጽሑፎችን ያቀርቡ ነበር። ባለፈው እሁድ በተወለዱ በ76 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተገልጧል። ስለ አቶ አሰፋ ጫቦ የሕይወት ታሪክ  ዶክተር ካሳ ከበደን በማናገር መክብብ ሸዋ ከዋሽንግተን ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።  

መክብብ ሸዋ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW