1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአንድ ለአንድ እንግዳችን አቶ ስለሺ ግርማ

ዓርብ፣ መስከረም 30 2018

በኢትዮጵያ የቱሪዝም አገልግሎት መስክ ከአፍላ ወጣትነታቸው ጀምሮ ጉልህ ሚና የነበራቸው ናቸው። ከሀገር አስጎብኚነት እስከ የሚንስትር ዴታነትም ደርሰዋል። ከዝግጅት ክፍላችን ጋር በነበራቸው የአንድ ለአንድ ቆይታ ከአፍላ የወጣትነት ጊዜያቸው ጀምሮ በቱሪዝም ኢትዮጵያ ውስጥ የነበራቸውን ቆይታ በጥቂቱም ቢሆን አካፍለውናል።

Äthiopien 2025 | Treffen mit Sileshi Girma, Staatsminister für Tourismus
ምስል፦ Ato Sileshi Girma/Ministerium für Tourismus Äthiopien

ከልጅነት እስከ እውቀት በቱሪዝም ውስጥ የኖሩት ሰው እና ቱሪዝም በኢትዮጵያ

This browser does not support the audio element.

በኢትዮጵያ የቱሪዝም አገልግሎት መስክ ከአፍላ ወጣትነታቸው ጀምሮ ጉልህ ሚና የነበራቸው ናቸው። ከሀገር አስጎብኚነት እስከ የሚንስትር ዴታነትም ደርሰዋል። ከዝግጅት ክፍላችን ጋር በነበራቸው የአንድ ለአንድ ቆይታ ከአፍላ የወጣትነት ጊዜያቸው ጀምሮ በቱሪዝም ኢትዮጵያ ውስጥ የነበራቸውን ቆይታ በጥቂቱም ቢሆን አካፍለውናል።

 

 

በልጅነታቸው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናትን በማስጎብኘት የጀመረው የቱሪዝም ፍቅር በትምህርታቸው ገፍተው የዩኒቨርሲቲ መምህር እስከ መሆን አድርሷቸዋል። በዚህ ያልተገቱት አቶ ስለሺ የአዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። አሁን የኢፌዲሪ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚንስትር ዴታ ናቸው ። አቶ ስለሺ ግርማ ።

ወርሃ መስከረም በተለይ በኢትዮጵያ የአዲስ ዓመት መባቻ እንደመሆኑ በርካታ ቱሪስቶች ይመጣሉምስል፦ Ato Sileshi Girma/Ministry of Tourism of Ethiopia


 

ወርሃ መስከረም በተለይ በኢትዮጵያ የአዲስ ዓመት መባቻ እንደመሆኑ እና የቱሪዝም ፍሰቱ ከወትሮ ልቆ የሚታይበት ወር እንደመሆኑ መጠን አቶ ስለሺ ስለአዲሱ የኢትዮጵያውያን ዓመት አቀባበል እና የመስከረም ወር እንዴት እንዳለፈም አጫውተውናል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያን ገጽታ ለማስተዋወቅ እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ፣ የዲጅታል ዘመን የቱሪዝም ኢትዮጵያ መስህብን ከቀደመው ዘመን ጋር እያነጻጸሩ አውግተውናል። 

የጸጥታ ችግር በኢትዮጵያ ያስከተለው መስተጓጎልበቱሪዝም መስክ ላይ ምን ችግር ፈጥሮ ይሆን ?ምስል፦ Ato Sileshi Girma/Ministry of Tourism of Ethiopia

 

የጸጥታ ችግር በኢትዮጵያ ያስከተለው መስተጓጎልበቱሪዝም መስክ ላይ ምን ችግር ፈጥሮ ይሆን ? የሚለውን ጨምሮ  የኢትዮጵያ ሆቴሎች እና ሪዞርቶች ደረጃ ፣ አገልግሎት እና የዋጋ ፍትሃዊነት በቱሪዝም ላይ የሚኢሳድረው ጫና ካለ እና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚና እና በቅርቡ ወደ አውሮጳ የተጓዙት የሉሲ እና ሰላም ቅሪተ አካላት ለኢትዮጵያ አዲስ የሚያመጡት ገጸ በረከት ካለ ተብለው ለተጠየቁት ሚንስትር ዴታው መልስ ሰጥተዋል። 
ታምራት ዲንሳ 
ጸሐይ ጫኔ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW