1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአወዛጋቢው ዳኛ ሹመት በአሜሪካ

ሰኞ፣ መስከረም 28 2011

በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ይሁንታ በአብላጫ የድምፅ ድጋፍ የሀገሪቱ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ እንዲሆኑ ብሬት ካቫኖ ተወስኖላቸው ቃለ መሐላ ፈፅመዋል። ካቫኖ ለዚህ ታላቅ ኃላፊነት ከታጩበት ጊዜ አንስቶ ከፍተኛ ተቃውሞ እና ክርክር ያስከተሉ ሲሆን ሹመታቸው በቃለ መሐላ ፀድቆም ተቃዎሞው መቀጠሉ ይሰማል።

USA Senat bestätigt umstrittenen Richterkandidaten Kavanaugh | Innenraum mit Abstimmungsergebnis
ምስል Reuters/Senate TV

የፍትህ አካሉ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ

This browser does not support the audio element.

ሀገሪቱን የሚያስተዳድሩት የሪፐብሊካን እና ዴሞክራት የሕዝብ እንደራሴዎች ክፉኛ የተከፋፈሉባቸው ብሬት ካቫኖ ከትናንት በስተያ ከተሾሙበት የከፍተኛው ፍርድ ቤት ዳኝነታቸው አረፍተ ዘመን ካልገታቸው በቀር ለቀጣይ 3 አስርት ዓመታት ሊከርሙበት እንደሚችሉ ነው የተነገረው። በፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጠቋሚነት የመጡት እና  የሪፐብሊካኖች ሙሉ ድጋፍ ያላቸው ዳኛ ሲመት ገለልተኛ ለሚባለው ለሀገሪቱ የፍትህ ሥርዓት ምን ማለት ይሆን?  ከዋሽንግተን የመገናኝ ብዙሃንን አስተያየት የቃኘው መክብብ ሸዋን ባጭሩ በስልክ አነጋግሬዋለሁ፤

መክብብ ሸዋ

ሸዋዬ ለገሠ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW