የአዉሮጳ ሕብረት ርዳታ ለኢትዮጵያ
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 4 2010ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ሕብረት፤ ኢትዮጵያ ከፀሐይ ለምታመነጨዉ የኤሌክትሪክ ኃይል ሥራ ማስፋፊያ የሚዉል የ10.35 ሚሊዮን ዩሮ ርዳታ ሰጠ። ሕብረቱ እርዳታዉን የሰጠዉ አካባቢን የማይበክል የንፁሕ እና የታዳሽ ኃይል አገልግሎትን ሥራ ላይ ለማዋል ባለዉ ዕቅድ መሠረት ነዉ። ለኢትዮጵያ በተመደበዉ ገንዘብ የሚሰራዉን የፀሐይ የኤልክትሪክ ኃይል ማመንጪያ ተቋምን የሚገነባዉ እና ቴክኒካዊ አገልግሎት የሚሰጠዉ የጀርመኑ የልማት ተራድኦ ድርጅት GIZ ነዉ። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ