የአዉሮጳ ሕብረት በጀት ለአፍሪቃ ቀንድ ስደተኞች
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 6 2010ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ሕብረት ለአፍሪቃ ቀንድ ሐገራት ስደተኞች እና ላስተናጋጆቻቸዉ ይረዳሉ ለተባሉ ፕሮጄክቶች ማስፈፀሚያ ከ176 ሚሊዮን ዩሮ በላይ መመደቡን አስታወቀ።ሕብረቱ የመደበዉ ገንዘብ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ6 የአፍሪቃ ሐገራት ሊሰሩ ለታቀዱ 13 ፕሮጄክቶች የሚዉል ነዉ።የአዉሮጳ ሕብረት ከአፍሪቃ ወደ አዉሮጳ የሚገቡ ስደተኞችን በያሉበት ለመገደብ ለአፍሪቃ መንግስታት የገንዘብ ድጋፍን ጨምሮ የተለያዩ ርዳታዎችን እያደረገ ነዉ።የሕብረቱን እርምጃ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች እየተቹት ነዉ።የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሤ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ገበያዉ ንጉሤ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ