የአዉሮጳ ኅብረትና የቱርክ የስደተኞች ሰፈራ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 27 2008ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ኅብረት ስደተኞች ወደ ግዛቱ እንዳይገቡ ለማገድ ከቱርክ ጋር በገባዉ ዉል መሠረት ስደተኞችን ከግሪክ ወደ ቱርክ እንዲሁም ከቱርክ ወደ ሌሎች የአውሮጳ ሃገራት የማሻገሩ ሥራ ጀምሮአል። በትናንትናዉ ዕለት 32 የሶሪያ ስደተኞች ከኢስታንቡል ቱርክ ወደ ሰሜንዊቷ የጀርመን ከተማ ሃኖቨር ገብተዋል። ፊንላንድም 11 የሶሪያ ስደተኞችን አስገብታለች። ስደተኞቹን ከአንድ ሃገር ወደ ሌላዉ ሃገር የመመለሱ ተግባር በርካታ ተቃዉሞ ና ትችት እየቀረበት ነዉ። ቅሪታቸዉን ከሚያሰሙት መካከል ለሰብዓዊ መብት መከበር የሚከራከሩ ድርጅቶች ግንባር ቀደሞች ናቸዉ። የቱርክና የግሪክ ነዋሪዎችም የስደተኞቹን ከቦታ ቦታ የማዘዋወር እርምጃ በሰልፍ እየተቃወሙት ነዉ። የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል፤ ቶማስ ቦርማን የዘገበዉን እንዲህ አቀናብሮታል።
ይልማ ኃይለሚካኤል
አዜብ ታደሰ