የአውሮጳ ህብረት ካውንስል ፕሬዚዳንት የቻይና ጉዞ
ሐሙስ፣ ኅዳር 22 2015![China Peking | Charles Michel und Xi Jinping](https://static.dw.com/image/63952338_800.webp)
ማስታወቂያ
ቻይና በሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ከህብረቱ ጋር ንግግር ለመቀጠል መስማማቱን በበጎ ጎኑ እንደሚቀበል የአውሮጳ ህብረት አስታወቀ። የህብረቱ ካውንስል ፕሬዚዳንት ቻርለስ ሚሸል ወደ ቻይና ተጉዘው ከፕሬዚዳንት ዢ ሺንፒንግ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ቻይና ከህብረቱ ጋር በንግድ ፣ በዓለማቀፍ ሰላም እና በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ለመነጋገር ብሎም አብሮ ለመስራት ፍላጎት አሳይታለች። የአውሮጳ ሕብረት እና የቻይና የጋራ ጉባኤ የህብረቱ ካውንስል ፕሬዚዳንት በተጨማሪ በታይዋን ፣ የሩስያ ዩክሬን ጦርነት እና ተያያዥ ጉዳዮች ተነጋግረዋል። የካውንስሉ ፕሬዚዳንት የቻይና ጉዞ አንድምታ በመለከተ የብራሰልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሴን በስልክ አነጋግረነዋል።
ታምራት ዲንሳ
ገበያው ንጉሴ
እሸቴ በቀለ