1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአውሮጳ ኅብረት የአጸፋ ርምጃ በአሜሪካን የታሪፍ ጭማሪ ላይ

ሐሙስ፣ መጋቢት 4 2017

የአውሮጳ ኅብረትን የንግድ ፖሊሲ የሚመራው የኅብረቱ ኮሚሽን እንዳለው አሜሪካን በብረት እና በአሉምንየም ላይ ለጣለችው የ25 በመቶ ታሪፍ ጭማሪ ፣ ኅብረቱ ከጎርጎሮሳዊው ሚያዚያ አንድ አንስቶ የአጸፋ ርምጃዎችን መውሰድ ይጀምራል ብሏል።

የአዉሮጳ ህብረት አርማ
የአዉሮጳ ህብረት አርማ ምስል፦ Nick Gammon/AFP/Getty Images

የአውሮጳ ሕብረት አጸፋዊ ምላሽ

This browser does not support the audio element.

 የአውሮጳ ኅብረት የአጸፋ ርምጃ በአሜሪካን የታሪፍ ጭማሪ ላይ 
አሜሪካ ከትላንት ጀምሮ በብረት እና በአሉምንየም ምርቶች ላይ ተግባራዊ ለምታደርገው አዲሱ ታሪፍ፣የአውሮጳ ኅብረት የአጸፋ ርምጃ እንደሚወስድ አስታወቋል። የአውሮጳ ኅብረትን የንግድ ፖሊሲ የሚመራው የኅብረቱ ኮሚሽን እንዳለው አሜሪካን በብረት እና በአሉምንየም ላይ ለጣለችው  የ25 በመቶ ታሪፍ ጭማሪ ፣ ኅብረቱ ከጎርጎሮሳዊው ሚያዚያ አንድ አንስቶ የአጸፋ ርምጃዎችን መውሰድ ይጀምራል ብሏል። የአውሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርዙላ ፎን ዴር ላየን ከአጸፋ ርምጃው ጋር፣ ኅብረቱ ለድርድር ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል።
በጉዳዮ ላይ ከብራስልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሴ ጋር ያደረግነው አጭር ቆይታ የማድመጫ ማዕቀፉን በመጫን እንድታደምጡት በአክብሮት እንጋብዛለን።
ገበያው ንጉሴ
ዮሃንስ ገብረእግዚአብሄር
እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW