1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአውሮጳ ኅብረትና ዩክሬን ያልመከሩበት የአሜሪካ ሩስያ የዩክሬን ጦርነት ማስቆሚያ እቅድ

ሐሙስ፣ ኅዳር 11 2018

ዩናይትድ ስቴትስ እና ሩስያ የዩክሬኑን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ የሰላም እቅድ ነድፈዋል።እቅዱ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ በትላልቅ ጉዳዮች ላይ በሰጥቶ መቀበል እንዲስማሙ ጥሪ ያቀርባል። የአውሮጳ ዲፕሎማቶች ግን እቅዱ የአውሮፓ ኅብረትና ዩክሬንን ባልተሳተፉበት የትም አይደርስም ሲሉ ቅሬታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው።

የአውሮጳ ኅብረት የውጭ ጉዳዮች ሃላፊ ካያ ካላስ
የአውሮጳ ኅብረት የውጭ ጉዳዮች ሃላፊ ካያ ካላስ ምስል፦ Nicolas Tucat/AFP/Getty Images

የአውሮጳ ኅብረትና ዩክሬን ያልመከሩበት የአሜሪካን ሩስያ የዩክሬን ጦርነት የሰላም እቅድ

This browser does not support the audio element.

ዩናይትድ ስቴትስ እና ሩስያ የዩክሬኑን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ እቅድ መንደፋቸው ተሰምቷል። አንድ  ለጉዳዩ ቅርበት አላቸው የተባሉ ሰውን ጠቅሶ አሶስየትድ ፕሬስ እንደዘገበው እቅዱ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ በትላልቅ ጉዳዮች ላይ በሰጥቶ መቀበል እንዲስማሙ ጥሪ ያቀርባል።

የአውሮጳ ዲፕሎማቶች ግን ይህን መሰሉ እቅድ የአውሮፓ ኅብረትዩክሬንን ባልተሳተፉበት የትም አይደርስም ሲሉ ቅሬታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው። የኅብረቱ የውጭ ጉዳዮች ሃላፊ ዛሬ የኅብረቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ብራሰልስ ውስጥ ስብሰባ ከመቀመጣቸው በፊት በሰጡት አስተያየት ሩስያ ሰላም ፈላጊ ከሆነች ቀደም ባሉት ጊዜያት ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ታደርግ ነበር ሲሉ ተናግረዋል። የፖላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩላቸው ኅብረቱ የሰላም ጥረቶችን እንደሚደግፉ አስታውቀው በጉዳዩ ላይ እኛም መምከር አለብን ብለዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ ዛሬ ከሚነጋገሩባቸው ጉዳዮች ውስጥ የአሜሪካንሩስያ የሰላም እቅድ ዋነኛው ነው። የሱዳን ጉዳይ ቤልጀየም የሚገኘውን የሩስያ ገንዘብ ለዩክሬን መስጠትና የመካከለኛው ምሥራቅ ጉዳዮች ይገኙበታል ። የብራሰልሱን ዘጋቢያችንን ገበያው ንጉሴን በዛሬው ስብሰባ ትኩረት በተሰጣቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ አነጋግረነዋል።

ገበያው ንጉሴ

ኂሩት መለሰ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ
ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW