1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮጳ ኅብረት በሱዳን እና ሊቢያ ጉዳይ መወያየቱ

ማክሰኞ፣ ግንቦት 6 2011

የአውሮጳ ሕብረት ውጭ ጉዳይ ሚንሥትሮች ትናንት ቤልጂየም መዲና ብራስልስ ውስጥ ባደረጉት ስብሰባ በዓለም ዙሪያ ለፀጥታ አሳሳቢ ባሏቸው ጉዳዮች ላይ መክረው ውሳኔ አስተላልፈዋል። የሊቢያ እና የሳህል ቃጣና የፀጥታ ኹኔታ በጥልቀት የተመረመረ ሲሆን፤ የሱዳን የፖለቲካ ኹኔታ ግን ብዙም አልተወራለትም።

Brüssel Treffen EU-Außenminister Federica Mogherini
ምስል picture-alliance/AA/D. Aydemir

የሊቢያ እና ሱዳን ጉዳይ በአውሮጳ ኅብረት

This browser does not support the audio element.

ሆኖም የሱዳን ወታደራዊ አዛዦች ከቀድሞው ፕሬዚደንት ዖማር ኧል በሽር የወሰዱትን ሥልጣን ወደ ሲቪሉ ማኅበረሰብ ማስረከብ እንደሚገባቸው የያዙት አቋም አኹንም የጸና መኾኑን ሕብረቱ ገልጧል። የገልፍ ተፎካካሪ ሃገራት በሱዳን ውስጣዊ የፖለቲካ ጉዳይ ጣልቃ መግባት ሥልጣኑን ወደ ሲቪሉ ማኅበረሰብ ለማሻገር የተጀመረው ጥረት ላይ መሰናክል  እንዳይፈጥር መስጋታቸው ተገልጧል። የአውሮጳ ሕብረት የውጭ ጉዳዮች ኃላፊ ፌደሪካ ሞጎሮኒን እዛው ብራስልስ ውስጥ ያነጋገራቸው ገበያው ንጉሤ ቀጣዩን ዘገባ አጠናቅሮልናል።  

ገበያው ንጉሤ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW