የአውሮፓና የላቲን አሜሪካና የካሬቢክ ሃገሮች ጉባኤ
ረቡዕ፣ ሰኔ 3 2007ማስታወቂያ
የአውሮፓ፤ የላቲን አሜሪካና የካሬቢያ ሃገሮች 2 ተኛው የመሪዎች የጋራ ጉባኤ ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ ዛሬ ተጀምሯል ። እስከ ነገ የሚዘልቀው የአትላንቲክ ማዶ ለማዶ ሃገራት ጉባኤ «የዜጎች ብልፅግና ዘላቂ ልማትና የወደፊት እጣ ፈንታ»በሚል መሪ ሃሳብ ላይ ያተኩራል ።በጉባኤው ላይ የ28ቱ የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት ፣እንዲሁም የ33ቱ የላቲን አሜሪካ እና የካሬብያን ሃገራት መሪዎችና የመንግሥታት ተወካዮች ተገኝተዋል ።የብራሰልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሴ ዝርዝር ዘገባ አለው ።
ገበያው ንጉሴ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሀመድ